���������������������������������������������
የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ቁጥር 1113/2011 ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ
ሰኔ 2017 ዓ.ም
መግቢያ/መነሻ ሁኔታ
ማሻሻያ ድንጋጌዎች
የአዋጁ አንቀጽ 8 ተሰርዞ በአዲስ አንቀጽ 8 ተተክቷል፡-
አንቀጽ 8፡- የቦርድ አባላት
ቦርዱ በሚከተለው ሁኔታ የሚሰየሙ ሰባት አባላት(በነባሩ 11 የነበረው) ይኖሩታል፦
ማሻሻያ
የአዋጁ አንቀፅ (59)(የምዝገባ ጥያቄን ስላለመቀበል) (1)(መ) ቀጥሎ የሚከተሉት አዲስ ንዑስ ፊደል ተራ (ሠ) እና (ረ)ተጨምረዋል፤
ማሻሻያ…
የአዋጁ አንቀፅ 61 (የምዝገባ ውጤት) ንዑስ አንቀፅ (5) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (5) ተተክቷል፡-
“5/ ማንኛውም ድርጅት፡-
ማሻሻያ…
ከአዋጁ አንቀፅ 61 ንዑስ አንቀፅ (5) ቀጥሎ የሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (6) ተጨምሯል፡-
የአዋጁ አንቀፅ 62 (የስራ ነጻነት) ንዑስ አንቀፅ (5) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (5) ተተክቷል፡-
ማሻሻያ
የአዋጁ አንቀፅ 62 ንዑስ አንቀፅ (6) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (6) ተተክቷል፡-
የአዋጁ አንቀፅ 62 ንዑስ አንቀፅ (7) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (7) ተተክቷል፡፡
ማሻሻያ…
የአዋጁ አንቀፅ 63 (የሀብት አሰባሰብና አስተዳደር) ንዑስ አንቀፅ (1)(ሐ) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (1)(ሐ) ተተክቷል፡-
��ማሻሻያ…�
የአዋጁ አንቀፅ 70 ርዕስ(ህልውናን ስለማረጋገጥ) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ርዕስ ተተክቷል፡-
የአዋጁ አንቀፅ 70(2) ቀጥሎ የሚከተሉት አዲስ ንዑስ ንዑስ አንቀፅ (3)፣(4)፣(5) እና (6) ተካተዋል፡-
ማሻሻያ…
ማሻሻያ…
ማሻሻያ…
የአዋጁ አንቀፅ 72 (አመታዊ የሒሳብ መግለጫና ምርመራ) ንዑስ አንቀፅ (2) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (2) ተተክቷል፡-
ማሻሻያ
የአዋጁ አንቀፅ 75 ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ አንቀፅ 75 ተተክቷል፡-
“75. የፋይናንስ ድጋፍ እና ባንክ ሒሳብ ስለመክፈት
የባንክ ሒሳብ ስለመክፈት
ማሻሻያ…
ማሻሻያ…
የአዋጁ አንቀፅ 77 (ምርመራ የማድረግ ስልጣን) ንዑስ አንቀፅ (4) እና (5) ተሰርው በሚከተሉት አዲስ ንዑስ አንቀፅ (4) እና (5) ተተክተል፡-
ማሻሻያ…
ማሻሻያ…
የአዋጁ አንቀፅ 78 ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ አንቀፅ 78 ተተክቷል፡-
“78. አስተዳደራዊ እርምጃ
1/ ባለሥልጣኑ ከሚከተሉት ጥፋቶች አንዱን ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ጥፋቶች ለፈፀመ ድርጅት የመጀመሪያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፡-
ሀ) በመተዳደሪያ ደንቡ ወይም በተሰጠው የውክልና ስልጣን ወይም በተፈቀደለት ዝርዝር መሰረት የማይመራና የማይንቀሳቀስ ከሆነ፤
ለ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ 65(1) መሰረት በስራ መሪነት ወይም በድርጅት የቦርድ ወይም የስራ አስፈፃሚ አባልነት መካተት የማይገባውን ሰው በአባልነት አካቶ ከተገኘ፤
ማሻሻያ…
ሐ) የምዝገባ ምስክር ወረቀቱን ግልፅ በሆነ ቦታ ላይ በዋናው መ/ቤት እና በቅርንጫፍ መ/ቤቶች አለመለጠፍ ወይም አለማስቀመጥ፤
መ) በባለስልጣኑ በሚቀርብለት ጥያቄ መሰረት ተገቢውን ምላሽና መረጃ በወቅቱ አለመስጠት ወይም አለማቅረብ፤
ሠ) በአዋጁ መሰረት ማቅረብ የሚገባውን ማንኛውንም የክንውን እና የፋይናንስ ሪፖርት በጊዜ ገደቡ አለማቅረብ፤
ረ) ንብረት እንዲሁም መተዳደሪያ ደንብን ጨምሮ ሌሎች ድርጅቱን የሚመለከቱ ሰነዶች አደራጅቶ በአግባቡ ካልጠበቀ ወይም ካልያዘ፣
ማሻሻያ
ሰ) በዚህ አንቀፅ ሌላ እርምጃ የሚያስወስዱ መሆኑ የተደነገገ ካልሆነ በስተቀር በዚህ አዋጅ ወይም አዋጁን ለማስፈፀም በወጣ ደንብ ወይም መመሪያ የተጣሉበትን ሌሎች ግዴታዎች በግልጽ የጣሰ ከሆነ፡፡
ሸ) በዚህ ንኡስ አንቀፅ ከተጠቀሱት ጥፋቶች ጋር በባህሪ ተመሳሳይ ወይም የሚቀራረቡ የሆኑ እና በባለስልጣኑ መመሪያ ሊወሰኑ የሚችሉ ጥፋቶችን መፈፀም፤
2/ በዚህ አንጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሰረት የሚሰጥ ማስጠንቀቂያ የተፈፀመውን የሕግ ጥሰት፣ ሊደረግ የሚገባውን ማስተካከያ እና በምን ያህል ጊዜ ውስጥ መስተካከል እንዳለበት በግልጽ በሚያሳይ ሁኔታ በፅሁፍ መሰጠት አለበት።
ማሻሻያ…
3/ ከሚከተሉት ጥፋቶች አንዱን ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ጥፋቶች የፈፀመ ድርጅት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ወይም የመጨረሻ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ይሰጠዋል፡-
ሀ) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) መሰረት የመጀመሪያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከተሰጠው በኋላ በአንድ የበጀት ዓመት ውስጥ ተመሳሳይ እርምጃ የሚያስወስድ ጥፋት ከፈፀመ፤
ለ) በዚህ አዋጅ ወይም አዋጁን ለማስፈፀም በወጣ ደንብ ወይም መመሪያ የተጣለበትን በፅሁፍ ለባለስልጣኑ ዕቅድ እና ሪፖርት የማቅረብ ወይም የማሳወቅ ግዴታ አሳማኝ በሆነ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር በጊዜ ገደቡ ካልተወጣ፤
ሐ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ 72 መሰረት ዓመታዊ የሂሳብ ምርመራ የማድረግ እና መግለጫ የመስጠት ግዴታውን ካልተወጣ፣
ማሻሻያ…
መ) የድርጅቱ አድራሻ ወይም ቢሮ ለውጥን ጨምሮ ማናቸውንም የድርጅቱን ለውጦች ለባለስልጣኑ አለማሳወቅ፣
ሠ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ 71 መሰረት የድርጅቱን የሂሳብ መዝገብ በአግባቡ የመያዝ ግዴታውን ካልተወጣ፣
ረ) የድርጅቱ ሰራተኞችና የስራ መሪዎች በድርጅቱ ውስጥ በተመደቡበት የስራ ምድብ ተገቢ ስራ እንዲሰሩ አለማድረግና ተገቢው አመራር አለመሰጠት፤
ሰ) ያለባለስልጣኑ እውቅና የድጋፍ ደብዳቤ የባንክ ሂሳብ መክፈት እና ባልተፈቀደላቸው ወይም ስልጣን በሌላቸው ግለሰቦች የባንክ ሂሳብን ማንቀሳቀስ፣
ሸ) በሀሰት የሌላ ሰውን ፊርማ አስመስሎ መፈረም፣ አለአግባብ ማህተም መጠቀም እና የጥቅም ግጭት የሚያስከትል ተግባር መፈጸም፤
ማሻሻያ…
ቀ) ያለባለስልጣኑ ፍቃድና እውቅና የሂሳብ ሰነዶች፣ ደረሰኞችን ማሳተም፣ ማህተም ማስቀረፅ፤
በ) ከባንክ ስርዓት ወይም በህግ ከተፈቀደው የገንዘብ ማንቀሳቀሻ መንገድ ውጭ ሂሳብ ማንቀሳቀስ ወይም ምንጩ ያልታወቀ ገንዘብ ከውጭ አገር ወይም ከአገር ውስጥ መቀበል ወይም ማንቀሳቀስ፤
ተ) ከባለስልጣኑ እውቅና ወይም ፈቃድ ውጭ የድርጅቱን ንብረት መሸጠ፣ ማስተላለፈ፣ ማስወገድ፣ መደበቀ ወይም ማሸሸ፤
ቸ) ሃብት የተገኘለትን ፕሮጀክት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ከተፈራረሙ በኋላ አለመፈፀም ወይም ከ6 ወር በላይ ሳይፈፅሙ መዘግየት፤
ኘ) በአዋጁ በተደነገገው መሰረት የአስተዳደራዊ ወጪው ከ20 ፐርሰንት በላይ ከሆነ፤
አ) በዚህ ንኡስ አንቀፅ ከተጠቀሱት ጥፋቶች ጋር በባህሪ ተመሳሳይ ወይም የሚቀራረቡ የሆኑ እና በባለስልጣኑ መመሪያ ሊወሰኑ የሚችሉ ጥፋቶችን መፈፀም፤
ማሻሻያ…
4/ በዚህ አንጽ ንዑስ አንቀጽ (3) መሰረት የሚሰጥ ማስጠንቀቂያ የተፈፀመውን የሕግ ጥሰት፣ ሊደረግ የሚገባውን ማስተካከያ፣ ማስተካከያው በምን ያህል ጊዜ ውስጥ መፈፀም እንዳለበት እና ጥብቅ ወይም የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሆኑን በግልጽ በሚያሳይ ሁኔታ በፅሁፍ መሰጠት አለበት።
5/ ከሚከተሉት ጥፋቶች አንዱን ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ጥፋቶች የፈፀመ ድርጅት እንደጥፋቱ መጠን በባለሥልጣኑ ውሳኔ ከሃምሳ ሺህ እስከ ሁለት መቶ ሃምሳ ሺ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡-
ሀ) የድርጅቱን ጥቅም ወይም የተጠቃሚዎችን ጥቅም ወይም የአባላትን ጥቅምና ፍላጎት የሚጎዳ ተግባር በግልፅ መፈፀም፤
ለ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ 76(3) መሰረት ስራው በኢትዮጵያውያን ሊሸፈን የማይችል ስለመሆኑ በባለስልጣኑ ሳይረጋገጥ የውጭ አገር ዜጋን እያሰራ ከተገኘ፤
ማሻሻያ…
ሐ) በዚህ አዋጅ መሰረት ለባለስልጣኑ የተሰጠ የክትትል እና ቁጥጥር ተግባርን ካስተጓጎለ ወይም ካደናቀፈ፤
መ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ 70 መሰረት የምዝገባ ምስክር ወረቀቱን በተገቢው ጊዜ ውስጥ ካላሳደሰ/ህልውናውን በጊዜ ገደቡ ውስጥ ካላረጋገጠ፤
ሠ) ከባለስልጣኑ ተገቢ ፈቃድ ወይም እውቅና ሳያገኝ በአደባባይ ህዝባዊ መዋጮ ያካሄደ ወይም ገቢ የሰበሰበ፤
ረ) በዚህ አዋጅ በተደነገገው መሰረት የፋይናንስ ገቢን ወይም ወደ ውጭ አገር ሲልክ በጊዜ ገደቡ ለባለስልጣኑ ካላሳወቀ፤
6) በዚህ አንቀፅ በተደነገገው መሰረት ሌሎች ጥፋቶችን የፈፀመ ድርጅት በአንቀፁ የተመለከተው እርምጃ የሚወሰድበት መሆኑ እንደተጠበቀ ሁኖ በባለስልጣኑ ውሳኔ በተጨማሪነት የገንዘብ መቀጮ ሊቀጣ ይችላል፡፡
ማሻሻያ…
7/ ከሚከተሉት ጥፋቶች አንዱን ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ጥፋቶች የፈፀመ ድርጅት ከአንድ ወር እስከ ስድስት ወር የሚደርስ የእግድ እርምጃ ይወሰድበታል፡-
ሀ) ከተመዘገበበት ወይም ከተፈቀደለት ዓላማ ውጭ ሲንቀሳቀስ ከተገኘ፤
ለ) ከተከለከለ የገቢ ምንጭ ሃብት ከተቀበለ ወይም ለተከለከለ የስራ መስክ ሃብት ከሰጠ፤
ሐ) የህዝብና የሀገርን ጥቅም የሚጎዳ ሕገ-ወጥ ተግባር መፈፀሙ ወይም በዚህ አይነት ተግባር ውስጥ መሳተፉ ከተረጋገጠ፤
መ) ሐሰተኛ ሪፖርት ወይም የተሳሳተ መረጃ ያቀረበ
ሠ) በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለአገር በቀል ድርጅቶች ፋይናንስ ወይም የቴክኒካል ድጋፎችን በመስጠት የፖለቲካ አድቮኬሲ፣ በመራጮች ትምህርት ወይም በምርጫ መታዘብ ወይም ማንኛውም ከምርጫ ጋር የተያያዘ ሥራ መስራቱ ወይም በዚህ ስራ ላይ መሰማራቱ ከተረጋገጠ፤
ማሻሻያ…
ረ) ከፖለቲካ ገለልተኛ ሳይሆን ኃላፊነት በጎደለው መልኩ መንቀሳቀሱ በግልፅ ከተረጋገጠ፤
ሰ) የበጀት ዓመቱ የአስተዳደራዊ ወጪው ከ40 ፐርሰንት በላይ ከሆነ፤
ሸ) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) መሰረት ጥብቅ ወይም የመጨረሻ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከተሰጠው በኋላ ወይም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (5) መሰረት የገንዘብ መቀጮ ከተቀጣ በኋላ ተመሳሳይ እርምጃ የሚያስወስድ ጥፋት በበጀት ዓመቱ ለሁለተኛ ጊዜ ከፈፀመ፤
8/ በዚህ አንጽ ንዑስ አንቀጽ (7) መሰረት የሚወሰድ የእግድ እርምጃ የተፈፀመውን የሕግ ጥሰት፣ እግዱ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ እና ሊደረግ የሚገባውን ማስተካከያ በግልጽ በሚያሳይ ሁኔታ በፅሁፍ መሰጠት አለበት።
ማሻሻያ…
9/ ከሚከተሉት ጥፋቶች አንዱን ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ጥፋቶች የፈፀመ ድርጅት እንዲሰረዝ ይደረጋል፡-
ሀ) ሃሰተኛ ሰነድ በማቅረብ ወይም አሳሳች መረጃ በመስጠት ወይም በማጭበርበር የተመዘገበ ከሆነ፤
ለ) በከፍተኛ ደረጃ የህዝብና የሀገርን ሰላም፣ ጥቅም ወይም ደህንነት አደጋ ላይ በሚጥል ህገ-ወጥ ተግባር መፈፀሙ ወይም መሳተፉ ከተረጋገጠ፤
ሐ) በወንጀል ድርጊት የተሰማራን ማንኛውም ሰው ወይም ቡድን በገንዘብ፣ በቁሳቁስ፣ በሃሳብ ወይም በቴክኒክ የሚደግፍ መሆኑ ከተረጋገጠ፣
መ) ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳቱ ከተረጋገጠ፤
ማሻሻያ…
ሠ) በወንጀል የተገኘ ሃብትን ህጋዊ አስመስሎ ካቀረበ ወይም ከተጠቀመ፤
ረ) ሰራተኞች ወይም የሥራ መሪዎች የድርጅቱን ገንዘብ ከመዘበሩ ወይም ከድርጅቱ ዓላማ ውጭ ለግል ጥቅሙ ካዋሉ እና ድርጅቱ የእርምት እርምጃ ካልወሰደ፤
ሠ) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (7) መሰረት የስድስት ወር የእግድ እርምጃ ተወስዶበት ተመሳሳይ እርምጃ የሚያስወስድ ጥፋት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በድጋሚ ከፈፀመ፤
10/ በዚህ አንጽ ንዑስ አንቀጽ (9) መሰረት የሚወሰድ የመሰረዝ እርምጃ የተፈፀመውን የሕግ ጥሰት በግልጽ በሚያሳይ ሁኔታ በፅሁፍ መሰጠት አለበት።
ማሻሻያ…
11/ በዚህ አንቀፅ መሰረት ድርጅቱን ለቅጣት የሚዳርጉ ጥፋቶች የፈፀሙ ወይም እንዲፈፀም ያደረጉ የድርጅቱ የስራ መሪዎች ወይም ሰራተኞች ወይም የሚመለከታቸው አካላት ላይ የድረጅቱ የበላይ አካል አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ ለባለሥልጣኑ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡
12/ በዚህ አንቀጽ መሰረት የሚወሰድ አስተዳደራዊ እርምጃ አግባብነት ባለው ሕግ መሰረት በድርጅት ወይም በድርጅት ኃላፊ ላይ ሊወሰድ የሚችል የወንጀል ተጠያቂነትን አያስቀርም፡፡
የአዋጁ አንቀፅ 85 ንዑስ አንቀፅ (6) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (6) ተተክቷል፡-
“6/ ምክር ቤቱ በባለሥልጣኑ ቦርድ ውስጥ ድርጅቶችን የሚወክሉ 2 ተወካዮችን ይመርጣል።”
ማሻሻያ…
7/ ምክርቤቱ ህጉን ተከትሎ በየዓመቱ የሚሰራቸው ስራዎችና የፋይናንስ አፈፃፀሙን በተመለከተ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ለባለስልጣኑ ያሳውቃል፤
8/ የምክርቤቱ ተጠሪነት ለምክር ቤቱ ጠቅላላ ጉባኤ ይሆናል፡፡
ከአዋጁ አንቀፅ 86 (የሲቪል ማኅበረሰብ ፈንድ) ንዑስ አንቀፅ (3) (ሐ) ቀጥሎ የሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (3) (መ) ተጨምራል፡-
“(መ) ከለጋሽ ድርጅቶች እና በድርጅቶች በራስ ተነሳሽነት ወይም በፍቃደኝነት ከሚደረግ ድጋፍ”
አመሰግናለሁ